የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር በአዲስ አበባ ባደረገው ቆይታ ከፌዴራል እና ከኦሮሚያ ክልል ባለስልጣናት ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቷል።


በዚህ ሳምንት በፕሬዝዳንት ጌታቸው ረዳ የሚመራው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ልዑክ ከፌዴራል መንግስት፣ ከፌደራል ኤጀንሲዎች እና ከኦሮሚያ ክልል መንግስት ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርጓል።

በጊዜያዊ አስተዳደሩ የተወያየባቸው ዋና ዋና ጉዳዮች የትግራይ ህገ-መንግስታዊ አስተዳደር መልሶ ማቋቋም፣ የተፈናቀሉ ዜጎችን ወደ ቀያቸው መመለስ እና ማቋቋም፣ የታገደው የትግራይ አመታዊ በጀት እንዲፈታ እና የትግራይን መልሶ መገንባት ይገኙበታል።

በቆይታቸውም ጊዜያዊ አስተዳደሩ በትግራይ መልሶ ግንባታ እና ማገገም ላይ ያተኮሩ ከተለያዩ የፌዴራል ኤጀንሲዎች ጋር የልምድ ልውውጥ አድርገዋል።

Leave a comment

Recent posts

Quote of the week

"People ask me what I do in the winter when there's no baseball. I'll tell you what I do. I stare out the window and wait for spring."

~ Rogers Hornsby